Tuesday, March 19, 2019

ዛሬ ስለ ፊንፊኔ ኣንድ ለማለት ፈለግን!

ከተወሰኑት ዓመታት በፊት በኢሳት ቲቪ ብዙ ጉድ መስማት ጀመርን። በኤርምያስ ኢልማ ለገሰ ዋቅጅራ በኩል በፊንፊኔ ዙሪያ ያለው የመሬት ቅርምትና ኣሳዛኝ የሶስት መቶ ሺህ ህዝብ መፈናቀል (ይህም የሰላሳ ቀበሌዎች ስሌት) ተተረከልን። እኛም ማንም ከዚያን በፊት በኣሃዝ ቀምሮ የነገረን ስላልነበር በኣግራሞት፣ በሃዘኔታ ኣዳመጥን፤ ኣነበብን።
ይሁን እንጂ የተነገረን እውነታ በድንገት ያመለጠ፣ ለፖለቲካ ፍጆታ ተብሎ እንጂ ከልብ በመነጨ ሃዘኔታ ኣልነበረም። ከፊንፊኔ ዙሪያ የተፈናቀሉ ኦሮሞዎች ከሶስት መቶ ሺህ እንደሚበልጡ የምናቀው ሲሆን ያንን ያህል ህዝብ ከቤቱና ከቄዬው ሲፈናቀል ምንም ያልመሰለው መንጋ ዛሬ እነዚያ ኦሮሞች በተፈናቀሉት ቄዬና ማሳ ላይ ኣጥር ኣጥረው ኣጥሩ ህገ ወጥ ነውና ይፍረስ ሲባል እዬዬውን ኣስቀድሞ ያቀልጣል።
ለመሆኑ የነዚያን ተፈናቃይ ገበሬ በሃዘኔታ ሲነግረን የነበረ መንጋ በምን ሞራልና ስብዕና ነው ዛሬ ለገ ጣፎ፣ ሱሊልታ፣ ሰበታ ወዘተ ህገ ወጥ ኣጥሮች ኣይፈርሱም ብሎ የሚጮሀው?
ይልቁንም ኦዴፓዎች ለህዝባችሁ ታመኑና የደረሰውን ግፍ በዝርዝር ኣስረዱን። ለናንተም ሃጢኣት መታጠቢያ ይሆናችሁ ዘንድና ለወራሪ መንጋውም ይገባው አንደሁ ብለን። ነገሩ የፈረሰውን ቄዬ የእልማን ገላን፣ የኢልማን ጉለሌ፣ የኢልማን ሳዴን ቱላማ በቁጥር እናውቃለን!
ቸር ይግጠመን!

No comments:

Featured Post

Raadiyoo Damablii gabaabaa

Odeeffaannoo baadiyyaa dhaqqabsuuf tamsaasa raadiyoon dambalii gabaabaa qabaachun murteessadha. Ummata keenyaa dammaqsuun maalumaafuu mur...